Support In Your Language
Amharic
አማርኛ
ከጾታዊ ጥቃት ለተረፉ ኢትዮጵያውያን የሚሰጥ የድጋፍ አገልግሎት**
እርስዎ ወይም የሚያውቁት ሰው ወሲባዊ በደል ደርሶቦት ከሆነ ወይም ማንኛውንም ወሲባዊ ድርጊት እንዲፈጽንሙ ከተገደዱ፣ እባኮትን በዚህ ላይ ብቻዎን እንዳልሆኑ ይወቁ። ደህንነትዎ መጠበቅ፣ ድጋፍ እና ክብር ማግኘት ይገባዎታል። እርዳታ ከፍያ ነጻ፣ ፈራጅነት ሳይኖበት፣ እና ለመጠቀም በጣም በሚመችዎ ቋንቋ ለእርስዎ ሊቀርብልዎ ይችላል።
አፋጣኝ እርዳታ
ወደ DC የተጎጂዎች የስልክ መስመር በ 1-844-443-5732 ይደውሉ ወይም የጽሁፍ መልእክት ይላኩ ወይም ደግሞ ከመብት ተሟጋች ጋር በግል ለመነጋገር በ dcvictim.org ቻት ያድርጉ። በ አማርኛ እና በ ሌሎች ቋንቋዎች አስተርጓሚዎች አሉ።
ተሟጋቾች ሊረዱዎት ይችላሉ:
– ወዲያውኑ የሕክምና አገልግሎት እንዲያገኙ (ከመረጡ፣ አንዳንድ ጊዜ የፎረንሲክ የሕክምና ምርመራ የሚበላአውን የ SANE ምርመራን ጨምሮ)።
– ዝግጁ ከሆኑ እና ሲሆኑ ለፖሊስ ሪፖርት ለማድረግ።
– መብቶችዎን እንዲረዱ እና አማራጮችዎን በሚስጥር እንዲያስሱ።
– ከአስተማማኝ መኖሪያ ቤት፣ ከህግ እርዳታ ወይም ከአማካሪ ጋር እንዲገናኙ።
የስደት ሁኔታ ምንም ይሁን ምን፣ ሁሉም ውይይቶች ሚስጢራዊ ናቸው፣ እና ሁሉም አገልግሎቶች ከክፍያ ነጻ የሚሰጡ ናቸው።
SANE የምርመራ አገልግሎቶች
SANE የምርመራ አገልግሎቶች በልዩ ሁኔታ በሰለጠኑ፣ የእርስዎን ከህክምና ጋር የተያያዙ ስጋቶችን ሊፈቱ የሚችሉ እንደዚሁም የተገኙ ማስረጃዎችን ሊሰንዱ እና ሊሰበስቡ በሚችሉ ነሶች የሚሰጡ ናቸው።
የምርመራውን ማንኛውም ክፍል እንዳይደረግልዎ ሊመርጡ እና SANE ም ምርመራውን እርስዎ በሚፈልጉት ፍጠነት እና በእርስዎ የተለዩ ፍላጎቶች መሰረት ያካሂዳል። ምርመራውን ማድረግ በምርጫዎ የሚካሄድ ነው።
የእርስዎ መብቶች
– በ አማርኛ አገልግሎቶችን እና ሰነዶችን የማግኘት መብት አልዎት።
-በማንኛውም አጋጣሚ የሰለጠነ አስተርጓሚ እንዲቀርብልዎ መጠየቅ ይችላሉ።
– የ SANE ምርመራዎችን ለማድረግ ያጋጠመውን ነገር ለፖሊስ ሪፖርት ማድረግ አይጠበቅብዎትም።
ለፖሊስ የደረሰውን ጥቃት ሪፖርት ማድረግ ከፈለጉ፣ በማንኛውም ጊዜ ወደ 911 ይደውሉ።
የስደተኝነት ሁኔታዎ በተመለከተ ስጋቶች ካልዎት፣ ይልዎትን መብት በተመለከተ፣ ወደ ዲሲ የተጎጂዎች ነጻ የስልክ መስመር በ 1-844-443-5732 በመደወል ከ መብት ተሟጋች ጋር መነጋገር ወይም ከስር ከተጠቀሱት ተቋማት ጋር መነጋገር ይችላሉ።
የእርስዎን ባህል እና ማህበረሰብ የሚረዱ ድርጅቶች
የሰው ማዕከል (TPC, The Person Center)
ከፆታዊ ጥቃት፣ የቤት ውስጥ ጥቃት እና ማሳደድ የተረፉ አፍሪካውያን ስደተኞችን እና ተፈናቃዮችን ይደግፋል። አገልግሎቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ:
– ለፍላጎትዎ የተዘጋጀ የጉዳይ አስተዳደርን
– የደህንነት እቅድን
– ስሜታዊ እና የህግ ድጋፍን
– በእያንዳንዱ እርምጃ ሚስጥራዊነትን እና ርህራሄን
እርዳታን እዚህ ጋር ይጠይቁ፡ [link]

Ayuda, Inc.
የሚከተሉትን አገልግሎቶች በማቅረብ አመኔታን ያተረፈ ድርጅት ነው፡
– በኢሚግሬሽን እና በፍርድ ቤት ጉዳዮች ላይ ለመርዳት የሚያስችሉ የህግ አገልግሎቶችን
– የአእምሮ ጤና ድጋፍ
– ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ስደተኞች የጉዳይ አስተዳደር

የኢትዮጵያ ማህበረሰብ ማዕከል (ECC, Ethiopian Community Center)**
የኢትዮጵያን ማህበረሰብ በሚከተሉት ጉዳዮች በማገልገል ላይ ነው:
– የባህል እና የማህበረሰብ ድጋፍ
– የግለሰብ የምክር አገልግሎት
– በሰነዶች እና በትርጉም እገዛ ማድረግ
– የወጣቶች ፕሮግራም እና ደህንነቱ የተጠበቀ ቦታ
